ማስታወቂያ: በዳግም ምደባ አዲስ ለተመደባችሁ ፍሬሽማን ተማሪዎች በሙሉ

በሳይንስና ከፍተኛ ት/ሚኒስቴር አማካኝነት በዳግም ምደባ ዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአንደኛ አመት ተማሪዎች የምዝገባ ቀን እስከ ዐ9/11/13 ዓ/ም ድረስ ብቻ መሆኑን እየገለጽን በተጠቀሱት ቀናት ለምዝገባ የሚያስፈልጉ የትምህርት ማስረጃችሁን እና ጉርድ ፎቶ ግራፍ በመያዝ በተፈጥሮ ሳይንስ መስክ የተመደባችሁ በዋናው ግቢ እና በማህበራዊ ሳይንስ መስክ የተመደባችሁ በኦዳያአ ግቢ ባሉ የሬጅስትራርና አሉምናይ ዳ/ጽ/ቤት በአካል በመቅረብ እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን፡፡
ማሳሰብያ፡- ከተጠቀሱት ቀናት ውጪ ለምዝገባ የሚመጡ ተማሪዎችን የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ሬጅስትራርና አሉምናይ ዳይሬክቶረት ጽ/ቤት