የዲላ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላት በ2013 ዓ.ም. ዕቅድ አፈፃፀም እና በ2014 ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡

ዲ.ዩ. መሰከረም 20/2014 ዓ.ም. (ህ.ግ) በተቋማችን ያሉ ችግሮችን ሆነ ጠንካራ ስራዎችን አውጥተን ተነጋግረን ለድክመቶቻችን መፍትሄ÷ ጠንካራ ጎናቻችንን ደግሞ ለማስቀጠል የካውስል አባላት ሚና የጎላ ነው ያሉን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዚዳንት ዶክተር ችሮታው አየለ ባለፉት ግዜያት ከካውሰል አባላት ጋር ለመገናኝትና ለመወያየት የኮቭድ-19 ተጽዕኖ ትልቅ ተግዳሮት እንደነበረ ተናግረዋል፡፡ የዬዘርፉ ኃላፊዎች ሪፖርታቸውን ያቀረቡ ሲሆን በየክፍሉ የተሰሩትንና ልሰሩ የታቀዱትን በሪፖርት አቅርበዋል፡፡ እንዲሁም በዬዘርፉ በበጀት ዓመቱ መልካም ተሞክሮዎችና ስኬቶችም የተዳሰሱ ሲሆን ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች ተብራርተዋል፡፡ የካውንስል አባላቱም በሪፖርት አቀራረብ መደሰታቸውን ገልፀው የተለያዩ ጥያቄዎችን ለየዘርፍ ኃላፊዎች አቅርበው ምላሽና ማብራሪያ የተሰጠባቸው ሲሆን በ2014 የበጀት ዓመት የተሳካ ስራ ለመስራት ተነጋግረዋል፡፡