በኮንፈረንሱ የSTEM ሴንተር በሀገር ደረጃም ሆነ በዩኒቨርሲቲው በቅርብ ጊዜያት የተጀመረ ቢሆንም ወደፊት በሳይንሳዊ ጥናት ለሀገራችን ዕድገትና ብልጽግና ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።
ኮንፈረንሱ "Challenges and prospects of STEAM Eduction in Ethiopia " በሚል መሪ ቃል ለሚቀጥሉት ሁለት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን በፕሮግራሙም የተለያዩ ጥናቶች ቀርበው ውይይት እንደሚካሄድባቸው ለማወቅ ተችሏል።
በዚህ በመጀመሪያው አገር አቀፍ የSTEM ምርምር ኮንፈረንስ ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣ የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር እንግዶች ፣ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ተመራማሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።