

ዲ.ዩ፡- ጥቅምት 15/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል ከ45 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገዛው የ‹ሲ.ቲ ስካን› ማሽን ስራ መጀመሩ ተገለጸ፡፡ ሆስፒታሉ የህክምና ስራዎቹን ለማሳለጥ እና ተደራሽነት ለማስፋት ከሚጠቀመው ዘመናዊ የሕክምና መሳሪያዎች አንዱ መሆኑን ነዉ የተገለጸው። በዩኒቨርሲቲው የሕክምና እና ሳይንስ ኮሌጅ እና ጠቅላላ ሆስፒታል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ምጽዋ ሩፎ ሆስፒታሉ ከጌዴኦ ዞን፣ ኦሮሚያ እና ሲዳማ አጎራባች ክልሎች ለሚመጡ ከፍተኛ ቁጥር ላለው ሕብረተሰብ የሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቅሰዋል፡፡ ለሕብረተሰቡ ከሚሰጣቸው የህክምና አገልግቶች በተጨማሪ ሆስፒታሉ በጤና ዘርፍ ተማሪዎችን በተለያዩ የሕክምና ሙያ መስኮች ተቀብሎ እያስተማረ እና እያሰለጠነ እንደሚገኝም ዶ/ር ምፅዋ ገልፀዋል፡፡ እሳቸው አክለውም አዲስ የተገዛው ‹ሲ.ቲ ስካን› በዚህ ሳምንት ስራ ጀምሯል ብለዋል፡፡ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ጠቅላላ ሆስፒታል የተግባር እና ስልጠና ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቢኒያም ወያ በበኩላቸው ‹‹በሆስፒታሉ ስንጠቀምባቸው ከነበሩ ማሽኖች ራጅ፣አልትራሳውንድ እና ሌሎች በደረጃ ከፍ ያለውን ሲ.ቲ ስካን ስራ መጀመሩ ተቋሙን አንድ ርምጃ ወደ ፊት የሚያሻግር›› መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
Public and International Relations Directorate
P.O.Box: 419
E-mail: pirdir@du.edu.et
Phone: +251461310001
: +251463312459
The website Developed by DUICT Business App Dev't