
በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ሀገር አቀፍ ወስዳችሁ፣ በአቅም ማሻሻያ (remedial) ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ወደ ዲላ ዩኒቨርሲቲ የምትገቡበት ቀን ከመጋቢት 14-15/2015 ዓ.ም መሆኑን እንገልፃለን።
ለምዝገባ ስትመጡ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት እና የ8ኛ ክፍሌ ካርድ ዋናውን እና የማይመለስ አንድ ፎቶ ኮፒ፣ 3x4 የሆነ አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣ የትራስ ጨርቅ፣ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን፡፡
#ማሳሰቢያ፦ ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም በአጠቃላይ ስድስት ሺህ ዘጠና አምስት (6,095) ተማሪዎችን ተቀብሎ የሚያስተምር ይሆናል።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አሉምናይ ዳይሬክቶሬት ፅ/ቤት