በሁለት ዙር ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተጠናቋል፤ ተማሪዎችም ወደየአካባቢያቸው ተሸኝተዋል

ዲ.ዩ፤ ሐምሌ 28/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፤ በአገር አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ በሁለት ዙሮች ሲሰጥ የቆየው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በሁለት ዙር ሲሰጥ የቆየው ብሄራዊ ፈተና መጠናቀቁን አስመልክቶ፤ ችሮታው አየለ (ዶ/ር)፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እንዲሁም ወ/ሮ ፈንቱ ኤልዶ፣ በትምህርት ሚኒስቴር የስርዓተ ትምህርት ዝግጅት ከፍተኛ ባለሙያ እና በፈተናው የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጉድኝት ማዕከል ኃላፊ በጋራ መገለጫ ሰጥተዋል፡፡

በታዳሽ ኃይል ልማትና የአቅም ግንባታ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተካሄደ

ዲ.ዩ፤ ሐምሌ 24/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት በይርጋጨፌ ከተማ ከጌዴኦ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ለተውጣጡ እማወራዎች በተደራሽ ኃይል ልማትና የአቅም ግንባታ ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል።
መድረኩ በታዳሽ ኃይል ልማትና የአቅም ግንባታ ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር ምክክር የተካሄደበት ሲሆን፤ በመድረኩ ለተሳተፉ እማወራዎችም በማገዶ ቆጣቢ ምድጃ አሰራርና አጠቃቀም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቶበታል።

የ12ኛ ክፍል ፈተና አስፈፃሚዎች በጌዴኦ ዞን የሚገኙ የትክል ድንጋይ መካነ-ቅርሶችን ጎበኙ

ዲ.ዩ፤ ሐምሌ 23/2015 ዓ/ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ለ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተመድበው የፈተና ሂደቱን ሲያስፈጽሙ የቆዩ መምህራን በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ወረዳ የቱሪስት መስህብ የሆኑትን የጨልባ ቱቲቲ ታሪካዊ ትክል ድንጋዮች ጎብኝተዋል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከጌዴኦ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ ጋር በመተባበር፤ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ ፈተና መጠናቀቁን ተከትሎ የጉብኝት መርሃግብር አዘጋጅተዋል።

የመጀመሪያ ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መጠናቀቁን ተከትሎ ተማሪዎች ወደ አካባቢዎቻቸው እየተሸኙ ነው

ዲ.ዩ፤ ሐምሌ 21/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፡- የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መጠናቀቁን ተከትሎ ተማሪዎች ወደ አካባቢዎቻቸው እየተሸኙ ነው።
በአገር አቀፍ ደረጃ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ እየተሰጠ የሚገኘው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሶስቱም ጊቢዎች ለሶስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ ቆይቶ፤ የመጀመሪያ ዙር ማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ትላንት በነበረ የከሰአት የፈተና መርሃግብር መጠናቀቁ ይታወሳል።

በመጀመሪያ ዙር የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች ገለጻ ተሰጠ

ዲ.ዩ፡- ሐምሌ 18/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ):- የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መሰጠት ከተጀመረ ሁለተኛ ዙር በሆነው የዘንድሮው ፈተና መርሃግብር በዲላ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ የመጀመሪያ ዙር ማለትም የማሕበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ስለ ፈተና አሰጣጥና በግቢ ውስጥ ስለሚኖራቸው ቆይታ ገለጻ (Orientation) ተደርጎላቸዋል፡፡

የመጀመሪያ ዙር የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ከትላንት ጀምሮ ወደ ዲላ ዩኒቨርሲቲ እየገቡ ነው።

ዲ.ዩ፡- ሐምሌ 17/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በዘንድሮ የትምህርት ዘመን በመጀመሪያው ዙር (ማህበራዊ ሳይንስ) የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ከትላንት ጀምሮ ወደ ዩኒቨርሲቲ እየገቡ ነው። ዲላ ዩኒቨርሲቲ በሁለቱም ዙር 17 ሽህ አካባቢ ተማሪዎች ተቀብሎ ይፈትናል።
የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎቹ ዛሬ ተጠቃለው የሚገቡ ሲሆን የቅድመ ፈተና ገለፃ (Orientation) ነገ ይሰጣል።

Pages