የዲላ ዩኒቨርሲቲ በፋይናንስ አሰራርና አስተዳደር ዙሪያ ስልጠናና ምክክር መድረክ አደረገ፡፡

ዲ.ዩ መስከረም 13/2014 ዓ.ም (ህ.ግ) ሀገር ልታድግና ወደ አለመችበት ደረጃ ልትደርስ የምትችለው ያላትን ሀብትና ንብረት በአግባቡ ስትጠቀም ነው ያሉን ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስ/ተማ/አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንትና የፕሬዝዳንቱ ተወካይ በዩኒቨርሲቲው ያሉ የፋይናንስ፣ የግዥ፣ የኦዲት፣ የዕቅድና የሚመለከታቸው ባለሙያዎችን ስልጠና መስጠት ያስፈለገው በሦስቱም ግቢዎች ያልተማከለ አሰራር ለመዘርጋት የሚደረግውን ጥረት ለማሳለጥ ነው ብለዋል፡፡
በዋናነት አሉ ዶ/ር ዳዊት በሦስቱም ግቢዎች በጄጂ የተመደቡ ሰራተኞችን ከነባር ሰራተኞች ጋር በስራ የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉና የሦስቱም ግቢዎች አሰራር አንድ ወጥ እንዲሆን ታስቦ ነው ብለዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሪፌራል ሆስፒታል በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የሲቲ ስካን (CT Scan) ማሽን አስገባ::

ዲዩ መስከረም 14/2014(ህ.ግ) አብዛኛውን ጊዜ የሪፌር ምክንያት ሆኖ የቆየውን ሲቲ ስካን ማሽን የህብረተሰብን ችግር በመረዳት መግዛቱን የተናገሩት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ሪፌራል ሆሰፒታል ም/ኘሬዝዳንት ዶ/ር ሰላማዊት አየለ በዚህ CT Scan ማሽን እጦት በርካታ የአከባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ መጉላላት ይደርስባቸው እንደነበር ገልፀው ማሽኑ የጌዴኦ ዞንን ጨምሮ እስከ ሞያሌ ድረስ ላሉ አጎራባች ማህበረሰብ ትልቅ አገልግሎት የሚሰጥና በዘርፉ ብቸኛ አገልግሎት ሰጪ ማሽን ያደርገዋል ብለዋል፡፡
ይህ ማሽን በተለይም የትራፊክ አደጋ ለደረሰባቸዉ ታካሚዎች፣ ለካንሰር ሕክምና እና ለሌሎችም በሽታዎች ምርመራ የሚያገልግልና ለዘርፉም ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ገልፀዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ እና ሪፌራል ሆስፒታል ወደ 5 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የምርምርና የህክምና ዕቃዎችን ድጋፍ አደረገ።

ዲ.ዩ መስከረም 12 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዪኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል 8 ለሚሆኑ የመንግስት ተቋማት ወደ 5 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የህክምና ዕቃዎችና የቢሮ መገልገያ መሳሪያዎችን ድጋፍ አደረገ።
ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስ/ተማ/አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት እና የዪኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ተወካይ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅና እና ሪፌራል ሆስፒታል ማኔጅመንት አጥንቶ ባቀረበው ጥናት መሰረት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት በሙሉ ልብ አፅድቆ በዛሬው ቀን እነዚህን ድጋፎች ለባለድርሻ አካላት እንዲሰጥ መወሰኑን ገልጸው ወደፊትም ይህን መሰሉ ድጋፍ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ተኮር ሬዲዮ ጣቢያ (FM 89.00) የሥራ አመራር ቦርድ የ2013 ዓ.ም የበጀት ዓመት የእቅድ ክንውን ሪፖርት እና የ2014 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ውይይት አደረገ::

ዲ.ዩ ነሐሴ 10/2014 ዓ.ም (ህ.ግ) ሬዲዮ ጣቢያው ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፎ አሁን ላለበት ደረጃ መብቃቱን የገለጹት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እና የሬዲዮ ጣቢያው የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ችሮታው አየለ ሬዲዮ ጣቢያው ከአማርኛ በተጨማሪ በአካባቢው በሚነገር በጌዴኦኛ ቋንቋ ፕሮግራም ስርጭት እንደሚያደርግ ገልጸው በኦሮሚኛና በሲዳሚኛ ቋንቋዎች የስርጭት ፕሮግራሙን ለማስፋት እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በዩኒቨርሲቲው ያሉት ኮሌጆች፣ የሥራ ክፍሎች እና የምርምር ማዕከላት ሥራቸውን በሬዲዮ ጣቢያው እንዲያስተላልፉ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ለግቢውና ለአካባቢው ማህበረሰብ ተደራሽ እንዲሆን ይሰራል ያሉት ዶ/ር ችሮታው የህዝብ ፍላጎትን ለማውቅ አስፈላጊ የዳሰሳ ጥናት ተደርጎ በቀጣይ አዳዲስ ፕሮግራሞችን ለመቅረጽ ብሎም አሁን ያሉትን ፕሮግራሞች የይዘት ማስተካከያዎችን ለማድረግ ጥረት ይደረጋል ብለዋል፡፡

ማስታወቂያ

በትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች በክረምት ፕሮግራም ትምህርታችሁን ሲትከታተሉ ለነበራችሁ እና በዲላ ዩንቨርሲቲ በጊዜያዊነት ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ሪፌራል ሆስፒታል አመራሮችና ሠራተኞች አዲሱን ዓመት በበጎ ፍቃድ ስራ መቀበላቸው ተገለፀ::

ዲ.ዩ መስከረም 02/2014 ዓም (ህ.ግ) ትልቁ ደስታና ዕርካታ የሰው ልጅን በመርዳት የሚገኘውን ውጤት ማየት ነው ያሉን ዶክተር ሰላማዊት አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ሪፌራል ሆስፒታል ም/ኘሬዝዳንት መላውን ሠራተኛ እንኳን ለ2014 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ ብለው የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሠራተኞች ከበጎ ፍቃደኛ ግለሰቦችና ተቋማት ጋር በመተባበር አዲሱን አመት በአዲስ ራዕይና በአዲስ ተግባር መጀመራቸው እንዳስደሰታቸው ተናግረዋል:: 

የአዲሱ ዓመት ክብረ በዓል ከታካሚዎች÷ ከጎዳና ልጆችና ከአቅመ ደካማ እናቶችና አባቶች ጋር በመሆን በሆስፒታል ቅጥር ግቢ የተከበረ ሲሆን በዕለቱም የተዘጋጀውን ማዕድ በጋራ በመቋደስና ለጎዳና ልጆች ከበጎ ፍቃደኞች የተሰበሰበውን ልብስ በማደል ተከብሮ መዋሉን ዶ/ር ሰላማዊት ገልፀዋል:: 

እንዲህ አይነት ተግባር በጥራትና ቁጥጥር ማሻሻያ  ጽ/ቤት ከሚሰሩ የጥራት ለውጥ ሥራዎች አንዱ የሆነው የራህራሄና አክብሮት ህክምና (CRC) አገልግሎት አካል ነው ብለዋል:: 

ዲላ ዩኒቨርሲቲ በክረምት የበጎ-ፈቃድ ሥራ የአቅመ ደካሞችን ቤቶች ግንባታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር አከናወነ፡፡

ዲ.ዩ. ጳጉሜ 04 ቀን 2013 ዓ.ም (ሕ.ግ) የአዲስ ዓመት መልካም ምኞት መግለጫ መልዕክት በማስተላለፍ ንግግራቸውን የጀመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ የበጎ ፈቃድ ሥራው በያዝነው ክረምት ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ የሆነ ገንዘብ በመመደብ በወናጎ ወረዳ 7 ቤቶች እንዲሁም በዲላ ከተማ 6 ቤቶች በድምሩ 13 ቤቶችን በ15 ቀናት ውስጥ ለተቸገሩ ቤተሰቦች ገንብቶ በማስረከብ በኢኮኖሚ አቅማቸው የተጎዱ ወገኖችን ለመደገፍ ታስቦ የተጀመረ ፕሮግራም መሆኑን ገልጸዋል፡፡  ለመርሃ ግብሩ መሳካት ድጋፍ ያደረጉትንና በዕለቱም ተገኝተው ሥራውን በጋራ ያስጀመሩትን የዲላ ከተማ እና የወናጎ ወረዳ አስተዳደር ካቢኔ አባላትን አመስግነው ቤት ለሚታደስላቸው ቤተሰቦችም እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ ዶ/ር ችሮታው አያይዘውም እንዲህ ዓይነት ተግባር በቀጣይ አመትም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የ2013 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ መዝጊያ ስነ-ስርዓት አከናወነ፡፡

ዲ.ዩ ጳጉሜ 03/2013 ዓ.ም (ህ.ግ) በቀጣይ ሁለት ዓመታት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን እንተክላለን ያሉት በፕሮግራሙ የተገኙት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ እንደ ሀገር “ኢትዮጵያን እናልብሳት” በሚል መሪ ቃል በዚህ ዓመት በተካሄደው የአረንጓዴ አሻራ የማኖር ፕሮግራም ዩኒቨርሲቲው በንቃት ሲሳተፍ መቆየቱን ገልፀው በዚህም 121 ሺህ ምግብ ነክ ያልሆኑ፣ 100 ቀርከሀ፣ 8040 ምግብ ነክ የሆኑ እና ተቋሙ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት የሚገኘው ምርጥ የቡና ዘር 247 ሺህ በአጠቃላይ ከ376,000 በላይ ችግኞችን በዩኒቨርሲቲው እና አካባቢው መተከሉን ተናግረዋል፡፡

ጌዴኦ እና አካባቢው አረንጓዴ እንደሆነ የሚታወቅ ቢሆንም የበለጠ አልምተን ለሀገራችን አረንጓዴ አሻራ የማኖሩን ስራ በእጅጉ እናግዛለን ያሉት ዶ/ር ችሮታው ለቀጣይ ዓመት የሚተከሉ ችግኞችን የማፍላት ሥራ ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም አሳውቀዋል፡፡

Pages