በዲላ ከተማ እየተካሄደ ባለው የመጽሐፍት ኤግዚቢሽን በተለያዩ ትምህርት ቤቶች የንባብ ክበባት ተመስርተዋል::

ዲዩ የካቲት 14 ቀን 2014 ዓ.ም. (ህ.ግ.) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጽሐፍት ኤጀንሲ እንዲሁም ከደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክ/መ/ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር “መጽሐፍት ለዕውቀት ገበታ፤ መዛግብትና የጽሁፍ ቅርሶች ለዘመን ትውስታ” በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ፕሮግራም ዛሬም ቀጥሎ ውሏል። በዛሬው ውሎ የትምህርት ቤቶች የንባብ ክበባትን በመመስረት፣ በማደራጀት እና ልምድ በመለዋወጥ ተግባራት በማተኮር ስራዎች ተከናውነዋል፡፡
በእለቱ ንግግር ያደረጉት የዲላ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከፍያለው ራቦ እንኳን ብዙ ምሁራን ወዳፈራው ዲላ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በሰላም መጣችሁ ሲሉ እንግዶችን ተቀብለዋል።

"መፃሕፍት ለእውቀት ገበታ፤ መዛግብት እና የጽሑፍ ቅርሶች ለዘመን ትውስታ" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ታላቅ የንባብ ሣምንት በዲላ ከተማ እንደቀጠለ ነው::

ዲ.ዩ የካቲት 13/2014ዓ.ም (ሕ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርስቲ ፤ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ መፃሕፍት ኤጀንሲ እና ደቡብ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መንግስት ባህልና ቱሪዝም ጋር በመተባበር የተዘጋጀው የንባብ ሣምንት አካል የሆነው በጌዴኦ ዞን ዲላ ማረሚያ ቤት የንባብ ክበብ ምሰረታና ተከናውኗል።
የንባብ ሳምንቱ መርሃ-ግብር ዛሬ ቀጥሎ ሲውል በጌዴኦ ዞን ባህል አደራሽ የሥነ-ጽሑፍ መድረክ በዛሬው ዕለት ተከናውኗል፡፡
"የሰው ልጅ በሆነ አጋጣሚ ወንጀል ሊሰራ ይችላል" ያሉት ኢንስፔክተር ትዕግስት ሮቤ የዲላ ማረሚያ ተቋም ኃላፊ መስሪያ ቤታቸው ከተመሠረተበት 1942 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ታራሚዎችን አንጾና አስተምሮ ወደ ማህበረሰቡ የመቀላቀል ስራውን እንደ ቀጠለ ገልፀዋል፡፡

መጻሕፍት ለእውቀት ገበታ፣ መዛግብትና የጽሑፍ ቅርሶች ለዘመን ትውስታ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ታላቅ የመጽሐፍ ኤግዚብሽን በዲላ ከተማ ተጀመረ።

ዲ.ዩ የካቲት 12 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት ኤጀንሲ እና ከደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግስት ባሕልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ታላቅ የንባብ ሳምንት፣ የቡክፌር ፣የኤግዚብሽን እና የፓናል ውይይት ዛሬ በዲላ ከተማ በይፋ ተከፍቷል።
የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የዲላ ከተማ ከንቲባ ክቡር አቶ ተስፋጽዮን ዳካ እንኳን ወደ አረንጓዴዋ ሻላይቱ ዲላ በሰላም መጣችሁ በማለት መልዕክታቸውን ካስተላለፉ በኃላ ይህ የንባብ ሳምንት አላማው የትውልዱን የንባብ ባህል በማጎልበት ትውልዱን ብቁ ዜጋ እንዲሆን ማስቻል እንደሆነ ተናግረው ፕሮግራሙ ወጣቱ ትውልድን ከደባል ሱስ ወደ መጻሕፍት ማንበብ እንዲያዘነብል የማድረግ ትልቅ አቅምና ጉልበት ያለው ዝግጅት እንደሆነ ተናግረዋል።

ለዲላ ዩኒቨርሲቲ እና አካባቢው ማህበረሰብ በሙሉ

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመፃሕፍት ኤጀንሲ እና ከደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግስት ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በመተባበር
“መጻሕፍት ለእውቀት ገበታ፤ መዛግብትና የጽሁፍ ቅርሶች ለዘመን ትውስታ”
በሚል መሪ ቃል ከየካቲት 12-16/2014 ዓ.ም የሚከበር የንባብ ሳምንት፣ የቡክፌር፣ የኤግዚብሽን እና የፓናል ውይይት ፕሮግራም በዲላ ከተማ አዘጋጅቷል፡፡
‹ፕሮግራሙ›

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ ከ221 ሺህ ብር በላይ ድጋፍ አደረገ።

ዲ.ዩ የካቲት 9 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ በምዕራብ ጉጂ ዞን አባያ ወረዳ በመልማት ላይ የሚገኝ የስንዴ እርሻ በስንዴ ዋግ በሽታ በመጠቃቱ ከ221ሺህ ብር በላይ የሚሆን የአይነትና የስልጠና ድጋፍ አደረገ።
የዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክተር አቶ ክብሩ አለሙ ከዩኒቨርሲቲው የተደረገውን ድጋፍ ባስረከቡበት ወቅት እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደምም ለአካባቢው ማህበረሰብ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ እንደነበር ገልጸው ዛሬ ደግሞ አርሶ አደሩ የስንዴ እርሻው በስንዴ ዋግ በመጠቃቱ የአባያ ወረዳ ግብርና ልማት ጽ/ቤት ላቀረበው የድጋፍ ጥያቄ አመራሩ ፈጣን ምላሽ በመስጠት በዲላ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር አካውንስል በተወሰነው ውሳኔ መሰረት ከ221 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ ድጋፍ መደረጉን ገልጸዋል።

CALL FOR PAPERS

DU organizes its 11th National Research Conference from 07-08 April 2022 and invites interested scholars to submit full-length completed research papers (Manuscripts) ONLY till 10 March 2022.

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሪፌራል ሆስፒታል አጠቃላይ ጉዳዮች ላይ ማህበረሰብ አቀፍ ወይይት ተካሄደ፡:

ዲ.ዩ፣ የካቲት 6/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሪፌራል ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥና አጠቃላይ ጉዳዮች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ማህበረሰብ አቀፍ ውይይት ተካሄደ። የሆስፒታሉን አጠቃላይ አመጣጥ፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ የተካሄደው ይህ ወይይት በቀጣይ ሊሰሩ የታቀዱ ተግባራትንም ያካተተ ነበር።
በመርሃ ግብሩ ላይ የመወያያ መነሻ ሪፖርት በዩኒቨርሲቲው የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሪፌራል ሆስፒታል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶክተር ሰላማዊት አየለ አማካይኝነት የቀረበ ሲሆን የውይይቱ ተሳታፊዎች የአዲሱን ሆስፒታል የግንባታ ሂደት ከጎበኙ በኋላ በሪፖርቱ ላይ ውይይት ተደርጎበታል።

Pages