በቤተ- ሙከራ አደረጃጀትና አጠቃቀም ዙርያ ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፦ ሕዳር 29/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ ማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የሳይንስ መምህራን በቤተ ሙከራ አደረጃጀትና አጠቃቀም ዙሪያ ስልጠና ተሰጥቷል።
በዩኒቨርስቲው የማሕበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተካልኝ ታደሰ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ፍኖተ ካርታ መሰረት በሀገር አቅፍ ደረጃ 55 በመቶ የተፈጥሮ ሳይንስ፣ እንዲሁም 45 በመቶ ደግሞ የማሕበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች እንዲሆን አቅጣጫ መቀመጡን አስታውሰዋል።
ይሁን እንጅ ባለፈው የትምህርት ዘመን በተደረገው የዳሰሳ ጥናት በጌዴኦ ዞን ባሉት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 26 በመቶ ተፈጥሮ ሳይንስ እና 74 በመቶ የማሕበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች እንደሆነ ውጤቱ ያሳያል።

ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተከብረ

ዲ.ዩ፦ ህዳር 27/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀንን "ሙስናን መታገል በተግባር" በሚል መሪ ቃል በልዩ ልዩ ዝግጅቶች አክብሮ ውሏል። በዓሉ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ19ኛ ጊዜ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ18ኛ ጊዜ ተከብሯል።
በዓሉን በንግግር የከፈቱት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ችሮታው አየለ (ዶ/ር) "አሁን ላይ እንደ ሀገር ሙስናን ለመከላከል እየተደረገ ያለውን ከፍተኛ ጥረት መላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ በንቃት በመከታተል እና በመደገፍ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመታገል ግንባር ቀደም ተዋናይ ሊሆን ይገባል" ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ምርምር ስራዎች ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

ምርምር ስራዎች ዙሪያ ውይይት ተካሄደ
ዲ.ዩ፦ ሕዳር 19/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምር እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ ቤት ከምርምርና ስርጸት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር በምርምር ስራዎች ዙርያ ሁለተኛ ዙር የውይይት መድረክ አካሂዷል።
ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በአሜሪካ ኢምባሲ ጋባዥነት ዘጠኝ የዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንቶች፣ አስራ አምስት ምክትል ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም ሁለት የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሙያዎች የተካተቱበት ጉብኝት በአሜሪካ በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች አደርገው መመለሳቸው ይታወሳል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ ‘‘ቴክኖ ሰርቭ’’ ግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

ዲ.ዩ፦ ህዳር 17/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ ‘‘ቴክኖ ሰርቭ’’ ከተባለ የግብረ ሰናይ ድርጅት ጋር በቡና ልማት ዙርያ አብሮ ለመስራት የስምምነት ሰነድ መፈራረሙ ተገልጿል።
ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት፤ አካባቢው እምቅ የቡና ሀብት ያለበት እንደመሆኑ መጠን ይህንን ለአከባቢው ማሕበረሰብ እና አገር እድገት ከፍተኛ ሚና እንዲኖረው በሳይንሳዊ ምርምር ለመደገፍ ሰፊ እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
አክለውም በቡና ልማት እስከ ሁለተኛ ዲግሪ ድረስ የትምህርት መርሐ ግብር በመክፈት፣ የምርምር ማእከል በመቋቋም፣ የችግኝ ማፍያ ጣብያዎችን በማቋቋም፣ ለአከባቢው አርሶ አደሮች አገልግሎት እየሰጠን ነው ብለዋል።

ለተከታታይ ሦስት ቀናት ሲካሄድ የነበረው የሳይንስ ሳምንት መርሃግብር ተጠናቀቀ

ዲ.ዩ፦ ህዳር 16/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምር እና ስርፀት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት "ሳይንስ ለምግብ ዋስትና እና ሉአላዊነት" በሚል መሪ ሐሳብ ሲከናወን የቆየው አራተኛው የሳይንስ ሳምንት ፍጻሜውን አግኝቷል።
በመርሃግብሩ ወቅት ንግግር ያደረጉት ዶ/ር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት በሀገራችን አመቱን ሙሉ የሚፈሱ ወንዞችንና ለም መሬት ይዘን የምግብ ዋስትናችንን ባለማረጋገጣችን ምክንያት በተጽእኖ ውስጥ እንድንወድቅ ሆነናል ብለዋል።
አያይዘውም ሀገሪቷ ያስተማረቻቸው ምሁራን በአገራችን ያለውን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና የተሻለ ስራ ለመስራት ጥናትና ምርምር ማድረግ እንዲሁም ጥናቱን ወደ ተግባር መለወጥ ይጠበቅብናል ሲሉ አሳስበዋል።

Dilla University receives educational simulator and machine donations

DU: Nov. 23, 2022 (P.I.R) Dilla University's College of Medical and Health Sciences received educational simulators and machine donations from Health Professional Education Partnership Initiative for its skill improvement center for medical students.
The surgical specialist and Health Professional Education Initiative coordinator at Dilla Center, Dr. Tesfaw Bekele, received the donations and submitted them to the skill hub coordinator. The donation includes dolls and machines with simulation equipment.

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርደ በዩኒቨርሲቲው ሁለንተናዊ ጉዳዮች ላይ ከተቋሙ ከፍተኛ አመራር ጋር ተወያየ

ዜና ትንታኔ ዲ.ዩ፡- ህዳር 03/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ በዩኒቨርሲቲው የ2014 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም እና የ2015 በጀት ዓመት እቅድ ላይ ዝርዝር ውይይት አካሄደ፡፡ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢዋ እና የከተማና መሰረተ-ልማት ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እና የስራ አመራር ቦርዱ አባላት በውይይቱ ተገኝተዋል፡፡ በእለቱ በዲላ ዩኒቨርሲቲ በአራቱ የምክትል ፕሬዝዳንት ፅ/ቤቶች፣ በህክማና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል እንዲሁም የፕሬዝዳንት ፅ/ቤት እና በስሩ ያሉ ባለ ብዙ ዘርፍ ፅ/ቤቶች ባለፈው አመት ያከናወኗቸው ተግባራት አፈፃፀም ሪፖርቶች ቀርበዋል፡፡ በዝርዝር ሪፖርቶቹ በአመቱ የታቀዱ፣ የተከናወኑ ተግባራት እንዲሁም በአፈፃፀም የተገኙ እምርታዎች እና ጉድለቶች ከተወሰዱ መፍትሄዎች ጋር በዝርዝር ተዳስሰዋል፡፡

የ‹ሲ.ቲ ስካን› ማሽን ስራ መጀመሩ ተገለጸ

ዲ.ዩ፡- ጥቅምት 15/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ጠቅላላ ሆስፒታል ከ45 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ የተገዛው የ‹ሲ.ቲ ስካን› ማሽን ስራ መጀመሩ ተገለጸ፡፡ ሆስፒታሉ የህክምና ስራዎቹን ለማሳለጥ እና ተደራሽነት ለማስፋት ከሚጠቀመው ዘመናዊ የሕክምና መሳሪያዎች አንዱ መሆኑን ነዉ የተገለጸው።
በዩኒቨርሲቲው የሕክምና እና ሳይንስ ኮሌጅ እና ጠቅላላ ሆስፒታል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ምጽዋ ሩፎ ሆስፒታሉ ከጌዴኦ ዞን፣ ኦሮሚያ እና ሲዳማ አጎራባች ክልሎች ለሚመጡ ከፍተኛ ቁጥር ላለው ሕብረተሰብ የሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ጠቅሰዋል፡፡

For all Regular Students of Dilla University

1) If you are a first-year (freshman) student and will start your second semester, you will report on Tikimt (ጥቅምት) 28 and 29, 2015 e.c.
2) Third year and above (3rd, 4th, and 5th) year students, we would like to inform you that the dates you will have to come and register at the university are Hidar (ህዳር) 05 and 06, 2015 e.c.
3) Students from the Health and Medical Sciences College will report according to the previous call.

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የመጀመሪያ ዙር በሰላም መጠናቀቁ ተገለፀ

ዲ.ዩ፦ ጥቅምት 02/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሶስቱም ግቢዎች ለሶስት ተከታታይ ቀናት የተሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና በሰላም ተጠናቋል።
በዋናው፣ ኦዳያአ እና ሐሴዴላ ግቢዎች ከተፈተኑት ከ16 ሽህ 800 በላይ ተማሪዎች መካከል ከቅርብ ርቀት የመጡት ተማሪዎች ወደየ አካባቢያቸው እየተሸኙ ሲሆን ሌሎች በተያዘላቸው የጉዞ መርሃግብር መሰረት የሚሸኙ ይሆናል።
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በዩኒቨርሲቲዎች እንዲሰጥ ከተወሰነ ጀምሮ በተቋሙ መዋቅር፣ የፀጥታ አካላት፣ ትምህርት ሚኒስቴር፣ እንዲሁም የአካባቢው አስተዳደር እና የሚመለከተው ባለ ድርሻ አካላት ሁለ ተሳትፎ ያደረጉበት ዝግጅት እንደ ነበር የገለፁት የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንትና የፕሬዝዳንቱ ተወካይ ዶ/ር ፍቃዱ ወ/ማርያም ናቸው።

Pages