የዲላ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ ስር የኪነ-ህንፃ ምህንድስና ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ተማሪዎችን አስመረቀ::

ዲ.ዩ መጋቢት 3/2014 ዓ.ም. (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ የኪነ ህንፃና የግንባታ ምህንድስና ትምህርት ቤት የኪነ-ህንፃ ምህንድስና (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል ተማሪዎችን አስመረቀ፡፡
የቴክኖሎጂ እና ምህንድስና ኮሌጅ መምህራንና ኃላፊዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች እንግዶችና ጥሪ የተደረገላቸው የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በታደሙበት ነው ምረቃቱ የተካሄደው።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ያደረጉ የተፈጥሮ ሀብት እና ግብርና ስራዎችን በተቀናጀ ሁኔታ እያከናወነ መሆኑን ገለፀ::

የዲላ ዩኒቨርሲቲ በመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ምደባ መሰረት የተግባር ተኮር (Applied) ዩኒቨርሲቲ ምደባ ውስጥ የተካተተ ነው። በዚህም መሰረት ዩኒቨርስቲው በትኩረት ከሚሰራባቸው መስኮች መካከል የግብርና እና ተፈጥሮ ሃብት አያያዝ ዋነኛው ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ዩኒቨርሲቲው ለአካባባው ማህበረሰብ ተደራሽ እንዲሆን የዕውቀት፣ የቴክኖሎጂና የክህሎት እገዛ ለማድረግ ከአካባባው ማህበረሰብ ፍላጐት ጋር የሚጣጣም ሥራ በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ዩኒቨርሲቲው የሚገኝበት አካባባ ጥምር ደን ግብርና እንዲሁም ከፊል አርብቶ አደር ሥልተ ምርት የሚከናወንበት በመሆኑ የልማት እገዛ ተግባራት ላይ ትኩረት ሰጥቶ ስራዎችን ያከናውናል፡፡ ከዚህ አኳያ በጥምር የደን ግብርና ሥራ ዙሪያ አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ የአካባቢ ዝርያዎች የመጠበቅና የዝርያ ማሻሻል ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሴት መምህራንን የምርምር ስራዎች ተሳትፎ ከፍ ለማድረግ ያለመ ምክክር ተካሄደ::

ዲ.ዩ. የካቲት 25/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሴት መምህራንን የምርምር ስራዎች ተሳትፎ ከፍ ለማድረግ ያለመ ምክክር ተካሄደ። የምክክር መድረኩ በዩኒቨርሲቲው የስርአተ-ፆታ ዳይሬክቶሬት ከምርምር እና ስርፀት ዳይሬክቶሬት ጋር በትብብር የተዘጋጀ ነው።
ያለ ሴቶች ተሳትፎ የሚያድግ ሀገርም ሆነ ህብረተሰብ የለም ያሉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴ/ህ/ወ/ጉ ዳይሬክተር ወ/ሮ አለሚቱ ብርሃኑ ጽ/ቤታቸው ዩኒቨርሲቲው በሚያዘጋጀው ስትራቴጂክ እና ዓመታዊ እቅዶች ላይ የሴት መምህራን እና ተመራማሪዎች እኩል ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ግቦች የበለጠ ትኩረት እንዲያገኙ እንሰራለን ብለዋል።
ኃላፊዋ አክለውም አመልካች ግቦችን በማስቀመጥ ሊለኩ የሚችሉና በውጤታማነት የሚተገበሩ እቅዶች እንዲዘጋጁና እንዲተገበሩ የሚያስችሉ ስራዎች ላይ እየተሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡

በዲላ ዩኒቨርሲቲ በሥነ ምግባር ምንነት ፅንሰ ሃሳብና አስፈላጊነት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አዲስ ለተቀጠሩ መምህራን ተሰጠ::

ዲ.ዩ. የካቲት 24/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ምግባር ምንነት ፅንሰ ሀሳብ እና አስፈላጊነት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና አዲስ ለተቀጠሩ መምህራን ሰጠ።  የዩኒቨርሲቲው የሥነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና ዳይሬክቶሬት ከሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክቶሬት ጋር በመሆን ነው ስልጠናውን ያዘጋጁት።
መምህራን ወደ ሥራ ከመሰማራታቸው በፊት ስለ ተቋሙ አጠቃላይ ገፅታና ባህሪ እንዲሁም የመንግስት ሠራተኞች የሚመሩበትና የሚተዳደሩበትን ህግና ደንቦች ማሳወቅ አስፈላጊ በመሆኑ ነው ስልጠናው የተሰጠው ተብሏል።
አዲስ ገቢ መምህራኑ በቀጣይ ሥራቸውን በአግባቡ እንዲሰሩ እና የተሻለ አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስችላቸውን ስልጠና አግኝተዋል ብለዋል፣ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የሰው ሀብት አስተዳደርና ልማት ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ፀጋ፡፡

126ኛ አመት የአድዋ ድል መታሰቢያ በአል ምክንያት በማድረግ ዶክተር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ያስተላለፉት መልዕክት

"ለመላው ኢትዮጵያዊያን፣ የኢትዮጵያ ወዳጆች፣ ለመላው ጥቁር ሕዝቦች፦ እንኳን ለ126ኛ አመት የአድዋ ድል መታሰቢያ በአል በሰላም አደረሳችሁ።
ይህንን በአል ስናከብር ጥንት አባቶቻችን የውጪ ጠላት በመጣ ጊዜ የውስጥ ልዩነታቸውን ወደ ጎን በመተው የውጪ ወራሪን በአንድነት ተፋልመው ድል እንዳደረጉ ሁሉ፣ ዛሬም ሐገራችን ወጥረው የያዟት ዘርፈ ብዙ የውጪ እና የውስጥ ጠላቶች አሏት። ዛሬም ሐገራችን አንድነቷን የሚፈታተን ፍልሚያ አለባት። ዛሬም ሐገራችን በአንድነት ቁመን እንድንታገልላት፣ ክብሯን፣ ነፃነቷን እንድናስጠብቅላት፣ በልዩነታችን እየተገፋፋን ለጠላት እድል ከማስፋት ይልቅ በአንድነታችን እየተደጋገፍን በህብረት ቁመን ዘርፈ ብዙ ድል እንድናጎናፅፋት ትሻለች።

የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞቾ ልማት ድርጅት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ትምህርት ድጋፍ ማዕከል ጋር በመተባበር ተማሪዎች ስልጠና ሰጠ።

ዲ.ዩ የካቲት 21/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞቾ ልማት ድርጅት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ትምህርት ድጋፍ ማዕከል ጋር በመተባበር ለተማሪዎች ስልጠና ሰጠ። ስልጠናው በአካል ጉዳተኝነት አና አካታችነት ጽንሰሀሳብ ዙሪያ ከየኮሌጁ ለተውጣጡ ጉዳት አልባ ተማሪዎች ተሠጥቷል፡፡
ተማሪዎች በጋራ በሚኖሩባቸው ቦታቸው፣ በመማሪያ ክፍላቸውና በእለት ተዕለት የጊቢ እንቅስቃሴያቸውም ሆነ ወደ ስራ አለም ሲቀላቀሉ በአገልግሎት አሰጣጥ ለሚያገኟቸው አካል ጉዳተኞች የሚኖራቸው መስተጋብር የተሻለ እንዲሆን ለማድረግ ታልሞ መዘጋጀቱን የልዩ ፍላጎት ት/ት ድጋፍ ማዕከል ዳይሬክተር ዶ/ር አባቡ ተሾመ ገልጸዋል።

በዲላ ዩኒቨርሲቲ በገቢ ግብር አዋጅ እና መመሪያዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ስልጠና ተሰጠ።

ዲ.ዩ የካቲት 21 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የኢፌዲሪ ገቢዎች ሚኒስቴር ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኙ የግዢ ፣ የፋይናንስና የውስጥ ኦዲት ባለሙያዎች በግዢ ግብር አዋጅ እና መመሪያዎች ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ስልጠና ተሰጠ።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ በግንባታ ላይ ያሉትን የአስተዳደር ህንፃ እና ሀሴዴላ ግቢ ጎበኘ::

ዲ.ዩ የካቲት 19/2014 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ እና የዩኒቨርሲቲው የበላይ አመራር የ2014 ዓ.ም የስድስት ወር እቅድ ክንውን ላይ ውይይት ካካሄደ በኋላ በኦዳያአ ግቢ የሚገኘውን የአስተዳደር ህንፃ እና የሀሴዴላ ግቢ አጠቃላይ የግንባታ ሂደት ጎብኝቷል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ አንጋፋ ከሚባሉ ዩኒቨርሲቲዎች አንዱ በመሆኑ ተቋሙን የሚመጥን የአስተዳደር ህንፃ መገንባቱ የሚያስደስት ነው ያሉት የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ እና የዩኒቨርሲቲው ስራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ የተከበሩ አቶ አብዮት ደምሴ፣ ግዙፉ የአስተዳደር ህንፃ ከዚህ በፊት የነበረውን የቢሮ እጥረት በመቅረፍ እና ምቹ የስራ ቦታ በመፍጠር እረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ብለዋል።
ቦርዱም ዩንቨርሲቲው የሚሰራቸው ስራዎች ላይ የቅርብ ክትትል እና ድጋፍ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ እፅዋት ጥበቃ እና ኢኮቱርዝም ማዕከል "የኢኮቱርዝም ልማት ለአከባቢ ብዝሃ ሕይወት ጥበቃ እና ለስራ ዕድል ፈጠራ" በሚል መሪ ቃል ውይይት አካሄደ::

ዲ.ዩ. የካቲት 19/2014 ዓ ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ እፅዋት ጥበቃ እና ኢኮቱርዝም ማዕከል "የኢኮቱርዝም ልማት ለአከባቢ ብዝሃ-ሕይወት ጥበቃ እና ለስራ ዕድል ፈጠራ" በሚል መሪ ቃል ውይይት አካሄደ። በውይይቱም የዲላ ከተማ፣ አባያ እና ዳራ ወረዳ አመራር አካላት ተሳትፈዋል።
የአካባቢ ብዝሃ-ሕይወት ለመጠበቅ የተፈጥሮን ጸጋ በምርምር በመለየት ወደ ሀብትነት መቀየር ይገባል። ስለሆነም አመራሮች እና የአከባቢው ማህበረሰብ ስለ ብዝሃ-ሕይወት ግንዛቤ እንዲኖራቸው ለማዲረግ፣ የኢኮቱርዝም አገልግሎትን ለማጠናከር ታስቦ ነው ይህ ውይይት የተዘጋጀው ብለዋል አቶ ምትኩ ማኑዳ የዲላ ዩኒቨርሲቲ እፅዋት ጥበቃ እና ኢኮቱርዝም ማዕከል ዳሬክተር።

Pages