የቅጥር እና የስራ ዝግጁነት ክህሎት የአሰልጣኞች ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፦ ሰኔ 03/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ"ደረጃ ዶት ኮም" ጋር በመተባበር ከተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ለተመረጡ መምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና ሰጥቷል። እነዚህ መምህራን በቀጣይ ለሚመረቁ ተማሪዎች የቅጥር እና የስራ ዝግጁነት ክህሎት የሚያሰለጥኑ መሆኑ ታውቋል።

የምርምር ሥራዎችን ተመሳስሎት ለመፈተሽ በሚያስችል የ"Turnitin " ሶፍትዌር ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ

ዲ.ዩ፡- ግንቦት 29/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፡- የምርምር ስራዎችን ተመሳስሎት ለመፈተሽ (Similarity Checker) በሚረዳ "Turnitin" በተሰኘ ሶፍትዌር ላይ የክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና ተሰጠ። ስልጠናው የተሰጠው ለድህረ-ምረቃ አስተማሪዎች፣ ለጆርናል ቦርድ አባላት፣ ለምርምር ጭብጥ መሪዎች እና ለምርምር ካውንስል አባላት ነው።

የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ያካሄዱትን የስራ ጉብኝት አጠናቀቁ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 27/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ የስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሲያካሂዱት የነበረውን የስራ ጉብኝት ማጠቃለያ መድረክ ዛሬ አካሂደዋል።

የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ልዩ ልዩ ዳይሬክተሮች ጋር ተወያዩ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 26/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ዘርፍ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያዩ።
ከትላትን ጀምሮ የመስክ ምልከታ በዲላ ዩኒቨርሲቲ እያካሄዱ ያሉት የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ በዛሬው የከሰአት ውሏቸው ከአካዳሚክ ዘርፍ ዳይሬክተሮች፣ ኮሌጅ ዲኖች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች እና ከየትምህርት ክፍሎች ከተወጣጡ መምህራን ጋር ነው ውይይት ያደረጉት።

Pages