የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ያካሄዱትን የስራ ጉብኝት አጠናቀቁ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 27/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ የስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ሲያካሂዱት የነበረውን የስራ ጉብኝት ማጠቃለያ መድረክ ዛሬ አካሂደዋል።
በጉብኝቱ በበጀት ዓመቱ የመማር ማስተማር፣ ጥናትና ምርምር፣ ማሕበረሰብ አገልግሎት፣ የመልካም አስተዳደር፣ የተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ዝግጅት እና የመሳሰሉትን ስራዎች የገመገሙ ሲሆን የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ በዩኒቨርሲቲው እየተከናወኑ ያሉ የልማት ስራዎችንም ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ልዩ ልዩ ዳይሬክተሮች ጋር ተወያዩ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 26/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ዘርፍ ማህበረሰብ አባላት ጋር ተወያዩ።
ከትላትን ጀምሮ የመስክ ምልከታ በዲላ ዩኒቨርሲቲ እያካሄዱ ያሉት የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ በዛሬው የከሰአት ውሏቸው ከአካዳሚክ ዘርፍ ዳይሬክተሮች፣ ኮሌጅ ዲኖች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች እና ከየትምህርት ክፍሎች ከተወጣጡ መምህራን ጋር ነው ውይይት ያደረጉት።
በውይይቱ የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) ከዩኒቨርሲቲው መምህራን ጋር ውይይት ማካሄድ ያስፈለገው በሀገሪቱ ቁልፍ ድርሻ ያለውን የተማረ የሰው ኃይል የሚፈጥሩ በመሆናቸው ነው ብለዋል።

የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የሁለተኛ ቀን የመስክ ምልከታ ዛሬም ተካሂዷል

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 26/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ከትላትን ጀምሮ የመስክ ምልከታ በዲላ ዩኒቨርሲቲ እያካሄዱ እንደሆነ መዘገባችን አይዘነጋም።
በቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ነገሬ ሌንጮ (ዶ/ር) የተመራው ቅኝት አድራጊ ቡድን ዛሬ ከሰአት በፊት በዲላ ዩኒቨርሲቲ እየተከናወኑ ያሉ ልዩ ልዩ የልማት ስራዎችን ተመልክቷል።

የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በዛሬ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ከሰአት በኋላ ቆይታቸው ልዩ ልዩ የመስክ ምልከታዎችን አካሂደዋል

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 25/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ስራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ምልከታ እያካሄዱ እንደሆነ ዛሬ ጧት መዘገባችን የሚታወስ ነው።
በጧቱ ክፍለ ጊዜ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ችሮታው አየለ (ዶ/ር) የዩኒቨርሲቲውን የ2015 በጀት ዓመት አበይት ተግባራት የተመለከተ ገለፃ የተደረገላቸው የቋሚ ኮሚቴው አባላት እረፋድ እና ከሰአት በኋላ በነበራቸው ጊዜ በዩኒቨርሲቲው ውስጥና ከዩኒቨርሲቲው ግቢዎች ውጪ ያሉ የስራ እንቅስቃሴዎችን ተዘዋውረው ቃኝተዋል።

የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ውይይት ተካሄደ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 24/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል ጉባዔ በዩኒቨርሲቲው የ2015 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ላይ ዛሬ ውይይት አካሂዷል።
በውይይት መድረኩ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈጻጸሞች ለመድረኩ ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል።
በእለቱ ቅድሚያውን ወስደው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ታምራት በየነ (ዶ/ር) በዘርፉ የተከናወኑ ስራዎችን ሪፖርት አቅርበዋል። በሪፖርታቸው፤ በአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ስር ባሉ ክፍሎች በዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራትን በየንዑስ ዘርፎች ቀንብበው አቅርበዋል።

የአባያ-ጫሞ ንዑስ ተፋሰስ ጥናት ፕሮጀክት ማስጀመሪያ ''ዎርክሾፕ'' ተካሄደ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 19/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም ውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ተፋሰስ አስተዳደር ፅ/ቤት በጋራ ትብብር የሚያከናውኑትን የውሃ ጥናት "ABAYA - CHAMO SUB-BASIN WATER ALLOCATION PLANNING" የማስጀመሪያ "ዎርክሾፕ" በዛሬው እለት በዲላ ዩኒቨርሲቲ ተካሂዷል።
በፕሮግራሙ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት ደረጀ ክፍሌ (ዶ/ር)፣ የጥናት ቡድኑ አባል፤ ባለፉት አራት አመታት የስምጥ ሸለቆ ተፋሰስን ትኩረት ያደረገ፤ ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ጋር በመቀናጀት በርካታ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን አንስተዋል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከ "ኢንፎ ማይንድ ሶሉሽንስ" ጋር የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ

ዲ.ዩ፦ ግንቦት 11/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ "ኢንፎ ማይንድ ሶሉሽንስ" ከተባለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ጋር በተመራቂ ተማሪዎች ዙሪያ አብሮ ለመስራት የሚያስችል የስምምነት ሰነድ መፈራረሙ ተገልጿል።
ማቴዎስ ሀብቴ (ዶ/ር )፣ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ፤ የተጠቀሰው ድርጅት በተመራቂ ተማሪዎች ዙሪያ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ጋር በትብብር ለመስራት የውል ስምምነት ላይ መድረሱን ነው የገለፁት።
ድርጅቱ በተለይም ከ"ኢትዬ ጆብስ" (ከኢትዮጵያ ስራዎች) ማኅበር ጋር በመተባበር ለተመራቂ ተማሪዎች የተለያዩ ስልጠናዎችን እየሰጠ ከቀጣሪ ድርጅቶች ጋር በመስራት ለምሩቃን በስፋት እድሎችን እየፈጠረ እንደሚገኝ ተገልጿል።

Pages