ዲላ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተናን ለመተግበር የሚያስችል የ"ኦንላይን" ፈተና አስተዳደር ስርአት አበለፀገ

ዲ.ዩ፦ ሚያዚያ 12/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ከያዝነው 2015 ዓ.ም ጀምሮ በአገር አቀፍ ደረጃ ይሰጣል ተብሎ እቅድ የተያዘለትን የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎች የመውጫ ፈተናን ለመተግበር የሚያስችል የ"ኦንላይን" ፈተና አስተዳደር ስርአት ማበልፀጉን ዲላ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።
የ"ኦንላይን" ፈተና አስተዳደር ስርአቱ (Online Examination Management System) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የኮምፒውተር ሳይንስ መምህራን በልፅጎ የዩኒቨርሲቲው ማኔጀመንት አባላት በተገኙበት ይፋ ተደርጓል።

በቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶአደሮች የቀርቀሃ ችግኝ ስርጭት ተካሄደ

ዲ.ዩ፦ ሚያዝያ 12/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት በጌዴኦ ዞን ቡሌ ወረዳ ለሚገኙ አርሶ አደሮች የቀረቀሃ ችግኝ ስርጭት አካሂዷል።
ደረጄ ክፍሌ (ዶ/ር) በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ኘሬዝዳንት፤ ከአምስት አመታት በፊት ጀጎ ላይ የነበረው የቀርቀሃ ደን የመጥፋት አደጋ አጋጥሞት እንደነበር አስታውሰው፤ ደኑን መልሶ ለማልማት የአምስት አመት ኘሮጀክት በመንደፍ ወደ ስራ በመገባቱን አሁን ላይ ወደ 4.5 ሄክታር የቀርከሃ ደን መልሶ ማልማት ተችሏል ብለዋል።

የአኘል ምርት በቡሌ ወረዳ የሚገኙ አርሶአደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው

ዲ.ዩ: መጋቢት 26/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት የአኘል ምርት በቡሌ ወረዳ የሚገኙ አርሶአደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ መሆኑን ገልጿል።
አቶ ተካልኝ ታደሰ የዳሬክቶሬት ፅ/ቤቱ ዳይሬክተር እንደገለጹት፤ በዩኒቨርሲቲው የማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት ስር ተደራሽ ከሚደረጉ ኘሮጀክቶች መካከል የመካከለኛውና የደጋማ አከባቢዎችን የሚሸፍነው የድንች፣ ቀርቀሃ፣ እንሰትና አኘል ልማት ናቸው ብለዋል።

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የጌዴኦ ዞን አስተዳደር በሰጠው መሬት ላይ በምርምር ያለማውን የእንሰት ችግኝ ለአርሶ አደሮች አሰራጨ

ዲ.ዩ፦ መጋቢት 22/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት በሳይንሳዊ መንገድ የበለጸጉ የእንሰት ችግኞችን በጌዴኦ ዞን ሁለት ወረዳዎች ውስጥ ለተመረጡ አርሶአደሮች አሰራጭቷል።
በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ኘሬዝዳንት ደረጄ ክፍሌ (ዶ/ር)፤ በምርምር ለምቶ ለአርሶአደሮች የተሰራጨው የእንሰት ችግኝ በዩኒቨርሲቲው ተደራሽ ከሚደረጉ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ ነው ብለዋል። ዲላ ዩኒቨርስቲ የአከባቢውን ማህበረሰብ ኑሮ በማሻሻል ገቢውን ለማሳደግ ተመሳሳይ በርካታ ስራዎችን መስራቱንም ገልፀዋል።

Dilla University Strengthens Women's Participation in Research and Leadership

D.U: March 25, 2023 (P.I.R.): Dilla University, Research and Dissemination Directorate, in collaboration with the NORHED ll ReRED project, held a discussion aimed at increasing the integrated research and leadership capacity of women academicians.
At the public lecture, Professor Alison Brown from Cardiff University, England, presented a public lecture titled "Enhancing Women's Participation in Collaborative Research and Academic Leadership."

የሴቶችን የምርምርና አመራርነት ተሳትፎ ማጎልበት እንደሚገባ ተገለጸ

ዲ.ዩ፦ መጋቢት 16/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ስርፀት ዳይሬክቶሬት ከNORHED ll ReRED ፕሮጀክት ጋር በመተባበር የሴቶችን የተቀናጀ የምርምርና አመራርነት አቅም ለማሳደግ ያለመ የውይይት መድረክ አካሂዷል።
በመድረኩ ከእንግሊዝ ሀገር ካርዲፍ ዩኒቨርሲቲ (Cardiff University) የመጡት ፕሮፌሰር አሊሰን ብራውን የሴቶችን የተቀናጀ የምርምርና አመራርነት ተሳትፎ ማጎልበት (Enhancing Women's participation in collaborative Research and Academic leadership) በሚል ርዕሰ ገለጻ አቅርበዋል።
ፕሮፌሰሯ በገለጻቸው እስከዛሬ በህይወት እና ሙያ መስካቸው ያካበቷቸውን ልምዶችና እውቀቶች ለመድረኩ ተሳታፊዎች አካፍለዋል።

የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ስራ አስኪያጅ ደራሲ የዝና ወርቁ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ከመምህራን እና ተማሪዎች ጋር ተወያዩ

ዲ.ዩ፦ መጋቢት 14/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ስራ አስኪያጅ ደራሲ የዝና ወርቁ በዲላ ዩኒቨርሲቲ ከመምህራን እና ተማሪዎች ጋር ትምህርታዊ ውይይት አካሄዱ። ደራሲ የዝና ወርቁ በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ዘመናዊ አጭር ልቦለድ ደራሲ ሲሆኑ የህዝብና ዓለምአቀፍ ግንኙነት ከፍተኛ ባለሙያ እና በልዩ ልዩ ጋዜጦች ዋና አዘጋጅ ሆነውም ሰርተዋል።
በዩኒቨርሲቲው ማኅበራዊ ሳይንስ እና ሥነ -ሰብዕ ኮሌጅ የአማርኛ ቋንቋና ሥነ- ጽሑፍ ትምህርት ክፍል ያሰናዳው ይህ ትምህርታዊ ውይይት ዛሬ በ"LH4" ሴሚናር አዳራሽ የተካሄደ ሲሆን መምህራን፣ ተማሪዎች እና የሥነ-ጽሁፍ አድናቂዎች ታድመውበታል።

Pages