ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢፌድሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ሲያካሂድ የነበረዉ የመጀመሪያው ሀገር ዓቀፍ የSTEAM Research ኮንፍረንስ ተጠናቀቀ፡፡

ዲ.ዪ ጥቅምት 20/2014 ዓ/ም /ህ.ግ/ STEAM ማዕከል በሀገር ዓቀፍ ደረጃ ሆነ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የተጀመረዉ በቅርብ ጊዜ ነዉ ያሉት ዶ/ር ዳዊት ሃዬሶ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስ/ተማ/አገ/ምክ/ፕሬዚዳንት እና የፕሬዝዳንቱ ተወካይ ያደጉ ሀገራት ተሞክሮ የሚያሳየን STEAM ላይ ጠንካራ ስራ መስራታቸዉ አሁን ላሉበት የእድገት ደረጃ እንዲደርሱ ከፍተኛ ሚና እነደነበረዉ ጠቅሰዉ እኛም ሀገራችንን ከድህነት እና ኋላ ቀርነት ለማላቀቅ በሳይንስና ቴክኖሎጂ እዉቀትና ክህሎት የታነጸ ትዉልድ ማፍራት ለነገ የማይባል ስራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የመጀመሪያው ሀገር አቀፍ የSTEM ምርምር ኮንፈረንስ መካሄድ ጀመረ። ዲ.ዩ ጥቅምት 19 ቀን 2014ዓ.ም (ህ.ግ)

በኮንፈረንሱ የSTEM ሴንተር በሀገር ደረጃም ሆነ በዩኒቨርሲቲው በቅርብ ጊዜያት የተጀመረ ቢሆንም ወደፊት በሳይንሳዊ ጥናት ለሀገራችን ዕድገትና ብልጽግና ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተገልጿል።
ኮንፈረንሱ "Challenges and prospects of STEAM Eduction in Ethiopia " በሚል መሪ ቃል ለሚቀጥሉት ሁለት ቀናት የሚካሄድ ሲሆን በፕሮግራሙም የተለያዩ ጥናቶች ቀርበው ውይይት እንደሚካሄድባቸው ለማወቅ ተችሏል።
በዚህ በመጀመሪያው አገር አቀፍ የSTEM ምርምር ኮንፈረንስ ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣ የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር እንግዶች ፣ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የመጡ ተመራማሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች አዲስ ከተሾሙት የጌዳኦ ዞን አስተባባሪ አባላት ጋር ትውውቅ እና በቀጣይ ሊኖር በሚገባው የስራ ግንኙነት ዙሪያ ውይይት አደረጉ::

ዲዪ ጥቅምት 15/2014 ዓ.ም. (ህዝብ ግንኙነት) በቀጣይ አብሮ ለመስራትና ለመተዋወቅ በመገናኝታችንና ህዝብን ለማገልገል በመመረጣችሁ በዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብና በራሴ ስም አንኳን ደስ አላችሁ ያሉት ዶክተር ችሮታው አየለ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዝዳንት አንድ ተቋም ከተቋቋመበት አካባቢና ማህበረሰብ ተለይቶ ምንም ስራ መስራት እንደማይችል ገልፀው የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለአከባቢው ማህበረሰብ በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት ሰፊ ስራ እየሰራ መቆየቱን ተናግረዋል::
አሁን ላይ ተቋሙ እየሰራ ያለውን ስራ ከታች ከህብረተሰብ አንስተን በማየት በቀጣይ ምን እንስራ÷ የተጀመሩትን ስራዎችን እንዴት እናስቀጥል÷ አዲስ ምን እንሰራ ብለን አብረን በመናበብ ለመስራት ይህ የውይይት መድረክ ሰፊ ፋይዳ አለው ብለዋል::

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል የአይን ህክምና ማዕከል ከኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በጌዴኦ ዞን ከ8 ወረዳዎች ለመጡ የማህበረሰብ ክፍሎች ነፃ የአይን ህክምና በይርጋ ጨፌ ከተማ እየሰጠ ይገኛል፡፡

ዲ/ዩ ጥቅምት 8/2014ዓ.ም (ህ.ግ) ጤናዉ የተጠበቀ ዜጋ ለሀገር እድገትና ብልጽግና ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር እዮብ አያሌዉ በዲላ ዩኒቨርሲቲ የአይን ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል እና ኦርቢስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ከዛሬ ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 6 ቀናት በአይን ሞራ ምክንያት ማየት ለተሳናቸዉ ወገኖች የአይን ህክምና እየሰጠ እንደሚገኝ ገልፀው የአይን ሞራ የሚከሰተዉ በእድሜ ምክንያት በመሆኑ ህመም ያለበት ሰዉ በጊዜ ወደ ጤና ተቋም በመምጣት መታከም ከቻለ የመዳን እድሉ ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ትምህርት ድጋፍ ማዕከል ከኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማዕከል (ECDD) ጋር በመተባበር ለአይነ ስውራን ተማሪዎች በውጤታቸው የተሻሉ እንዲሆኑ በጃውስ የታገዘ የኮምፒውተር ስልጠና ሰጠ፡፡

ዲ.ዩ. ጥቅምት 01/2014 ዓ.ም. (ህ.ግ.) የአካዳሚ ጉዳዮች ም/ኘሬዝዳንት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ነዲ ገቢሳ እናንተ መምህራን በመሆናችሁ ይህ አሁን ላይ የወሰዳችሁት መሰረታዊ የኮምፒውተር እውቀት ለስራችሁ ትልቅ እገዛ አለው ብለው የኮምፒውተር ዕውቀት በስልጠና ብቻ የሚገኝ ሳይሆን እለት ተእለት በሚደረግ ልምምድ የሚጎለብት በመሆኑ ትኩረት እንዲሰጥበት አሳስበዋል፡፡
እድሉ ከተሰጣቸው አይነ ስውራን ከማንኛውም የተሻለ ብቃትና ክህሎት እንዳላቸው ስለሚያምን እኔ አልገረምም ያሉን ደግሞ የትምህርትና ስነ-ባህሪ እንስቲትዩት ዲን ዶክተር መስፍን ሞላ ከዚህ በፊት የኔ መምህር የነበሩት የብዙ ሙያዎች ባለቤት እንደነበሩ አውስተው ለብዙዎች ውጤታማትም አርዓያ ነበሩ ብለዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብን ችግር በዘላቅነት ለመፍታት እየሰራ መሆኑ ተገለፀ፡፡

ዲ.ዩ. ጥቅምት 07/2014 ዓ.ም. (ህ.ግ.) ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተቋቋሙበት አከባቢ ያለውን የማህበረሰቡን ችግሮች በምርምርና በማህበረሰብ አገልግሎት መፍታት አንዱ የስራቸው አካል መሆኑን የተናገሩት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ኘሬዝዳንት ተወካይ ዶክተር ደረጄ ክፍሌ በይርጋጨፌና ኮቾሬ ወረዳዎች የደረሰውን የጎርፍ አደጋ አጥኝ በመመደብ የችግሩን መጠን በዝርዝር ለዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ካውንስል በማቅረብና ችግሩን በዘላቅነት ለማስቀረት ሰፊ ስራ እየተሰራ መሆኑን ዛሬ በኮቾሬ ተገኝተው ድጋፉን በሚያበረክቱበት ወቅት ተናግረዋል፡፡

በዲላ ዩኒቨርሲቲ የግዥና ንብረት አስተዳደር አሰራርን ለማዘመን ስልጠና ተሰጠ::

ዲ.ዩ. ጥቅምት 6 ቀን 2014 ዓ.ም (ሕ.ግ) ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከፌዴራል መንግስት የግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ጋር በመተባበር ለከፍተኛ ኃላፊዎች፣ የግዥ አጽዳቂ ኮሚቴዎችና ከተለያዩ የሥራ ክፍል ለተወጣጡ ባለሙያዎች በመንግስት ግዥ አስተዳደር ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፡፡
በስልጠናው ፕሮግራም ላይ የመክፍቻ ንግግር ያደረጉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ችሮታው አየለ የተቀላጠፈ አሰራር በተቋም ደረጃ ለማረጋገጥ ስልጠናው በክህሎትና በዕውቀት ደረጃ ግንዛቤ ለማስጨበጥ አሰፈላጊ መሆኑን ገልፀው እንደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም የግዥና ንብረት አስተዳደር አሰራር ሥርዓትን ዘመናዊ ለማድረግ ደንቦች፣ ሕጎችንና መመሪያዎች ተከትለን መሥራትና አሰራሩን ቀልጣፋ ማድረግ አለብን ብለዋል፡፡

14ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዲላ ዩኒቨርሲቲ በድምቀት ተከበረ።

ዲ.ዩ ጥቅምት 1 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) 14ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን "በአዲስ ምዕራፍ በተሟላ ሉዓላዊነት ለሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ" በሚል መሪ ቃል በዲላ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ ስነ ስርዓቶች ተከበረ።
በአገራችን አዲስ ካቢኔ ተዋቅሮ መንግስት በይፋ ስራ የጀመረበት ወር ላይ ይህን የሰንደቅ ዓላማ ቀን ማክበራችን ልዩ ያደርገዋል ያሉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሎታው አየለ ይህ ክቡር የሆነ ሰንደቅ ዓላማ በግዑዝ ሲታይ ከጨርቅ የተሰራ ይሁን እንጂ ውስጠ ሚስጥሩ ግን የኢትዮጵያ ማንነት መገለጫ የሆነ ብዝዎች የተሰውለት እና ብዝዎች ውድ ዋጋ የከፈሉለት ምልክት ከመሆኑም በላይ ለብዙ የአፍሪካ አገራት ጭምር ብሔራዊ ባንዲራ ሆኖ በማገልገል ላይ ያለ ሰንደቅ ዓላማ እንደሆነ ተናግረዋል ።

የኢትዮጰያ አካል ጉዳተኞች ልማት ማዕከል ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ፍላጎት ትምህርት ድጋፍ ማዕከል ከ140, 000 ሺህ ብር በላይ የሚያወጡ ለአካል ጉዳተኞች የትምህርት መርጃ ቁሳቁሰ ድጋፍ አደረገ::

ዲ.ዩ. መስከረም 28/2014 ዓ.ም (ህ.ግ) ድርጅቱ ላለፉት ሁለት ዓመታት በአካል ጉዳተኞች ላይ ድጋፍ በማድረግ እየሰራ እንደቆየ ያስታወሱት ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስ/ተማ/አገ/ምክ/ኘሬዝዳንት ለአካል ጉዳተኞች ስልጠናና ድጋፍ ከመስጠት አልፎ ለሌላው ማህበረሰብ በአካል ጉዳተኝነት ዙሪያ ግንዛቤ የማስጨበጡን ስራ በሰፊው መስራቱን ተናግረዋል::
ዶ/ር ዳዊት አክለው ድርጅቱ የተቋማችን አጋር በመሆን በተለይ አካል ጉዳተኞችን በግብዓት በመደገፍ ሰፊ ስራ እየሠራ ነው ብለዋል::

Pages