

ዲ.ዩ. መሰከረም 20/2014 ዓ.ም. (ህ.ግ) በተቋማችን ያሉ ችግሮችን ሆነ ጠንካራ ስራዎችን አውጥተን ተነጋግረን ለድክመቶቻችን መፍትሄ÷ ጠንካራ ጎናቻችንን ደግሞ ለማስቀጠል የካውስል አባላት ሚና የጎላ ነው ያሉን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዚዳንት ዶክተር ችሮታው አየለ ባለፉት ግዜያት ከካውሰል አባላት ጋር ለመገናኝትና ለመወያየት የኮቭድ-19 ተጽዕኖ ትልቅ ተግዳሮት እንደነበረ ተናግረዋል፡፡ የዬዘርፉ ኃላፊዎች ሪፖርታቸውን ያቀረቡ ሲሆን በየክፍሉ የተሰሩትንና ልሰሩ የታቀዱትን በሪፖርት አቅርበዋል፡፡ እንዲሁም በዬዘርፉ በበጀት ዓመቱ መልካም ተሞክሮዎችና ስኬቶችም የተዳሰሱ ሲሆን ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች ተብራርተዋል፡፡ የካውንስል አባላቱም በሪፖርት አቀራረብ መደሰታቸውን ገልፀው የተለያዩ ጥያቄዎችን ለየዘርፍ ኃላፊዎች አቅርበው ምላሽና ማብራሪያ የተሰጠባቸው ሲሆን በ2014 የበጀት ዓመት የተሳካ ስራ ለመስራት ተነጋግረዋል፡፡
ዲ.ዩ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ የ"ነጩ ፓስታ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት" ዘመቻ መቀላቀሉን መልዕክት በማስተላለፍ ንግግራቸውን የጀመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሎታው አየለ ይህ ሃገራዊ ዘመቻ የአሜሪካ መንግስት ይልቁንም ፕሬዝዳንቱ ሀገራችን ላይ የሚያደርጉትን ፍታዊ ያልሆነ ጫና እንዲቀንሱና ከእኛ ላይም እጃቸውን እንዲያነሱ ለማድረግ ታስቦ የተጀመረ ሃገራዊ ዘመቻ መሆኑን ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ከዚህ ቀደም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ሰላም በማስከበር ግዳጅ ላይ መስዋህትነት እየከፈለ ለሚገኘው የሀገር መከላኪያ ሠራዊት 30 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ድጋፍ በመለገሰ አጋርነቱን ማሳየቱን ገልጸው በቀጣይ ሳምንት ደግሞ ለተፈናቀሉ ወገኖች በአይነት ድጋፍ ለማድረግ እንደ ተቋም ዕቅድ መያዙን ገልፀዋል።
Public and International Relations Directorate
P.O.Box: 419
E-mail: pirdir@du.edu.et
Phone: +251461310001
: +251463312459
Dilla University
University of the Green Land!
The website Developed by DUICT Business App Dev't