Pages

የዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ3ኛ (PhD) እና የ2ኛ ዲግሪ የአዲስ ስርዓተ ትምህርቶች ግምገማ አውደ- ጥናት አካሄደ።

ዲ.ዩ መስከረም 22 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የስርዓተ ትምህርቶች የውስጥ እና የውጪ ግምገማ አውደ -ጥናት አካሄደ።
ወደ አውደ-ጥናቱ የመጡ እንግዶችና ተሳታፊዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የአካዳሚክ እና ምርምር ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌትነት መላኩ አውደ-ጥናቱ ለኮሌጁ የመጀመሪያው የሆነውን የ3ኛ ዲግሪ ፕሮግራም በሕብረተሰብ ጤና (PhD in Public Health) እና ለኮሌጁ 5ተኛ የሆነውን የ2ኛ ዲግሪ ፕሮግራም በአካባቢ ጤና (MPH in Environmental Health) ለመክፈት የተደረገ የካሪኩለሞች ግምገማ አውደ ጥናት መሆኑን አስታውቀዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ዶ/ር አበባየሁ ታደሴ እና ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳ አዲስ በተዋቀረው በደብብሕክ መንግስት ምስረታ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ሆነው ተሾሙ::

ዛሬ በተዋቀረው በደብብሕክ የመንግስት ምስረታ ላይ የክልሉ አፌ-ጉባኤ እና ምክትል አፌ-ጉባኤ እንዲሁም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር መሾሙ የሚታወቅ ሲሆን በርዕሰ መስተዳድሩ የተከበሩ አቶ ርስቱ ይርዳው አቅራብነት የክልሉ ካቢኔ አባላትና የፌደሬሽን ምክር ቤት ተወካዮች ተሰይመዋል::
ከዕጩዎች መካከል የዩኒቨርሲቲያችን የምርመርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት እና የብልፅግና ፓርቲ ተወካይ ዶ/ር አበባየሁ ታደሴ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ የመንገድና ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ እና የዩኒቨርሲቲያችን የሀገር በቀል ጥናት ተቋም (Indigenous Institute) ኃላፊ እና የኢዜማ ፓርቲ ተወካይ ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳ የክልሉ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል::

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ለኮቪድ-19 ሕክምና አገልግሎት የሚውሉ ግብዓቶችን Heart to Heart International ከተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት በድጋፍ መልክ አገኘ::

ዲ.ዩ. መስከረም 22 2014 ዓ.ም. የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል በአሜሪካን ሀገር በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከተቋቋመው Heart to Heart International ከተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት ለኮቪድ-19 ሕክምና አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ የህክምና ግብዓቶችን ድጋፍ እንደተደረገለት የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ሪፌራል ሆስፒታል ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሰላማዊት አየለ ገልጸዋል፡፡
ድጋፍ የተደረጉት ዕቃዎች በገንዘብ ስሰላ 5,030 የአሜሪካን ዶላር ማለትም ብር 231,000 ዋጋ የሚያወጡና የኮቪድ-19 ህክምና ላይ ለምንሰራቸው ስራዎች ጉልህ አስተዋጽኦ ያላቸው የህክምና ግብዓቶች መሆናቸውን ዶ/ር ሰላማዊት ተናግረው ለጠቋማችን ተልዕኮ ስኬት ከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር የሚደረጉ ትብብሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላት በ2013 ዓ.ም. ዕቅድ አፈፃፀም እና በ2014 ዕቅድ ላይ ውይይት አካሄዱ፡፡

ዲ.ዩ. መሰከረም 20/2014 ዓ.ም. (ህ.ግ) በተቋማችን ያሉ ችግሮችን ሆነ ጠንካራ ስራዎችን አውጥተን ተነጋግረን ለድክመቶቻችን መፍትሄ÷ ጠንካራ ጎናቻችንን ደግሞ ለማስቀጠል የካውስል አባላት ሚና የጎላ ነው ያሉን የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኘሬዚዳንት ዶክተር ችሮታው አየለ ባለፉት ግዜያት ከካውሰል አባላት ጋር ለመገናኝትና ለመወያየት የኮቭድ-19 ተጽዕኖ ትልቅ ተግዳሮት እንደነበረ ተናግረዋል፡፡ የዬዘርፉ ኃላፊዎች ሪፖርታቸውን ያቀረቡ ሲሆን በየክፍሉ የተሰሩትንና ልሰሩ የታቀዱትን በሪፖርት አቅርበዋል፡፡ እንዲሁም በዬዘርፉ በበጀት ዓመቱ መልካም ተሞክሮዎችና ስኬቶችም የተዳሰሱ ሲሆን ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሄ እርምጃዎች ተብራርተዋል፡፡ የካውንስል አባላቱም በሪፖርት አቀራረብ መደሰታቸውን ገልፀው የተለያዩ ጥያቄዎችን ለየዘርፍ ኃላፊዎች አቅርበው ምላሽና ማብራሪያ የተሰጠባቸው ሲሆን በ2014 የበጀት ዓመት የተሳካ ስራ ለመስራት ተነጋግረዋል፡፡

ዲላ ዩኒቨርሲቲ "ነጩ ፖስታ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት" ሃገራዊ ዘመቻን ተቀላቀለ።

ዲ.ዩ መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ የ"ነጩ ፓስታ ወደ ነጩ ቤተ-መንግስት" ዘመቻ መቀላቀሉን መልዕክት በማስተላለፍ ንግግራቸውን የጀመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ችሎታው አየለ ይህ ሃገራዊ ዘመቻ የአሜሪካ መንግስት ይልቁንም ፕሬዝዳንቱ ሀገራችን ላይ የሚያደርጉትን ፍታዊ ያልሆነ ጫና እንዲቀንሱና ከእኛ ላይም እጃቸውን እንዲያነሱ ለማድረግ ታስቦ የተጀመረ ሃገራዊ ዘመቻ መሆኑን ተናግረዋል። ፕሬዝዳንቱ አክለውም የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ከዚህ ቀደም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ሰላም በማስከበር ግዳጅ ላይ መስዋህትነት እየከፈለ ለሚገኘው የሀገር መከላኪያ ሠራዊት 30 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ድጋፍ በመለገሰ አጋርነቱን ማሳየቱን ገልጸው በቀጣይ ሳምንት ደግሞ ለተፈናቀሉ ወገኖች በአይነት ድጋፍ ለማድረግ እንደ ተቋም ዕቅድ መያዙን ገልፀዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ በፋይናንስ አሰራርና አስተዳደር ዙሪያ ስልጠናና ምክክር መድረክ አደረገ፡፡

ዲ.ዩ መስከረም 13/2014 ዓ.ም (ህ.ግ) ሀገር ልታድግና ወደ አለመችበት ደረጃ ልትደርስ የምትችለው ያላትን ሀብትና ንብረት በአግባቡ ስትጠቀም ነው ያሉን ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስ/ተማ/አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንትና የፕሬዝዳንቱ ተወካይ በዩኒቨርሲቲው ያሉ የፋይናንስ፣ የግዥ፣ የኦዲት፣ የዕቅድና የሚመለከታቸው ባለሙያዎችን ስልጠና መስጠት ያስፈለገው በሦስቱም ግቢዎች ያልተማከለ አሰራር ለመዘርጋት የሚደረግውን ጥረት ለማሳለጥ ነው ብለዋል፡፡
በዋናነት አሉ ዶ/ር ዳዊት በሦስቱም ግቢዎች በጄጂ የተመደቡ ሰራተኞችን ከነባር ሰራተኞች ጋር በስራ የልምድ ልውውጥ እንዲያደርጉና የሦስቱም ግቢዎች አሰራር አንድ ወጥ እንዲሆን ታስቦ ነው ብለዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ሪፌራል ሆስፒታል በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውን የሲቲ ስካን (CT Scan) ማሽን አስገባ::

ዲዩ መስከረም 14/2014(ህ.ግ) አብዛኛውን ጊዜ የሪፌር ምክንያት ሆኖ የቆየውን ሲቲ ስካን ማሽን የህብረተሰብን ችግር በመረዳት መግዛቱን የተናገሩት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ሪፌራል ሆሰፒታል ም/ኘሬዝዳንት ዶ/ር ሰላማዊት አየለ በዚህ CT Scan ማሽን እጦት በርካታ የአከባቢው ማህበረሰብ ከፍተኛ መጉላላት ይደርስባቸው እንደነበር ገልፀው ማሽኑ የጌዴኦ ዞንን ጨምሮ እስከ ሞያሌ ድረስ ላሉ አጎራባች ማህበረሰብ ትልቅ አገልግሎት የሚሰጥና በዘርፉ ብቸኛ አገልግሎት ሰጪ ማሽን ያደርገዋል ብለዋል፡፡
ይህ ማሽን በተለይም የትራፊክ አደጋ ለደረሰባቸዉ ታካሚዎች፣ ለካንሰር ሕክምና እና ለሌሎችም በሽታዎች ምርመራ የሚያገልግልና ለዘርፉም ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ገልፀዋል፡፡

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅ እና ሪፌራል ሆስፒታል ወደ 5 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የምርምርና የህክምና ዕቃዎችን ድጋፍ አደረገ።

ዲ.ዩ መስከረም 12 ቀን 2014 ዓ.ም (ህ.ግ) የዲላ ዪኒቨርሲቲ ሪፌራል ሆስፒታል 8 ለሚሆኑ የመንግስት ተቋማት ወደ 5 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ የህክምና ዕቃዎችና የቢሮ መገልገያ መሳሪያዎችን ድጋፍ አደረገ።
ዶ/ር ዳዊት ሀዬሶ የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስ/ተማ/አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት እና የዪኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ተወካይ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ጤናና ህክምና ሳይንስ ኮሌጅና እና ሪፌራል ሆስፒታል ማኔጅመንት አጥንቶ ባቀረበው ጥናት መሰረት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማኔጅመንት በሙሉ ልብ አፅድቆ በዛሬው ቀን እነዚህን ድጋፎች ለባለድርሻ አካላት እንዲሰጥ መወሰኑን ገልጸው ወደፊትም ይህን መሰሉ ድጋፍ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ተናግረዋል።

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ ተኮር ሬዲዮ ጣቢያ (FM 89.00) የሥራ አመራር ቦርድ የ2013 ዓ.ም የበጀት ዓመት የእቅድ ክንውን ሪፖርት እና የ2014 ዓ.ም ዕቅድ ላይ ውይይት አደረገ::

ዲ.ዩ ነሐሴ 10/2014 ዓ.ም (ህ.ግ) ሬዲዮ ጣቢያው ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፎ አሁን ላለበት ደረጃ መብቃቱን የገለጹት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት እና የሬዲዮ ጣቢያው የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ችሮታው አየለ ሬዲዮ ጣቢያው ከአማርኛ በተጨማሪ በአካባቢው በሚነገር በጌዴኦኛ ቋንቋ ፕሮግራም ስርጭት እንደሚያደርግ ገልጸው በኦሮሚኛና በሲዳሚኛ ቋንቋዎች የስርጭት ፕሮግራሙን ለማስፋት እየሰራ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በዩኒቨርሲቲው ያሉት ኮሌጆች፣ የሥራ ክፍሎች እና የምርምር ማዕከላት ሥራቸውን በሬዲዮ ጣቢያው እንዲያስተላልፉ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ለግቢውና ለአካባቢው ማህበረሰብ ተደራሽ እንዲሆን ይሰራል ያሉት ዶ/ር ችሮታው የህዝብ ፍላጎትን ለማውቅ አስፈላጊ የዳሰሳ ጥናት ተደርጎ በቀጣይ አዳዲስ ፕሮግራሞችን ለመቅረጽ ብሎም አሁን ያሉትን ፕሮግራሞች የይዘት ማስተካከያዎችን ለማድረግ ጥረት ይደረጋል ብለዋል፡፡

ማስታወቂያ

በትግራይ ዩኒቨርሲቲዎች በክረምት ፕሮግራም ትምህርታችሁን ሲትከታተሉ ለነበራችሁ እና በዲላ ዩንቨርሲቲ በጊዜያዊነት ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ

Pages