"በዩኒቨርሲቲያችን የመውጫ ፈተናን በአግባቡ ለመስጠት ሰፊ ዝግጅት እየተደረገ ነው" ማቴዎስ ሀብቴ (ዶ/ር) የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዝዳንት ተወካይ ዲ.ዩ፦ መጋቢት 8/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ከያዝነው 2015 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስትና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተግባራዊ ለማድረግ የታቀደውን የመውጫ ፈተና (Exit exam) ዲላ ዩኒቨርስቲ ለተመራቂ ተማሪዎቹ በ"ኦንላይን" ለመስጠት የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑ ተገልጿል። ማቴዎስ ሀብቴ (ዶ/ር) የዲላ ዩኒቨርስቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካይ፤ መንግስት ከትምህርት ጥራት ጋር ተያይዞ እንደ ሀገር ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን ለመቀነስ በማሰብ በመጪው ሐምሌ ወር በመንግስት እና በግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ የያዘለትን የመውጫ ፈተና ዩኒቨርሲቲው በብቃት ለመስጠት ሰፊ የዝግጅት ስራዎች እየሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።
ዓለማቀፉ የሴቶች ቀን "ማርች 8"ን ተንተርሶ በ"እናት" መፅሐፍ ላይ ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ ዲ.ዩ መጋቢት 8/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በዲላ ዩኒቨርስቲ "ማርች 8" የሴቶች ቀን በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ112ኛ ጊዜ “ፈጠራና ቴክኖሎጂ ለጾታ እኩልነት” በሚል መሪ ቃል ተከብሯል። በእለቱም ጭብጡን ሴትነትን ከቤተሰብ ህይወት እስከ ማህበረሰባዊ ሁለንተናዊ ጉዳዮች በይኖ የሚዳስስ "እናት" የተሰኘ መፅሐፍ ተመርቆ ለውይይት ቀርቧል። መፅሐፉን በዲላ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ዶ/ር ይሁኔ አየለ ናቸው የፃፉት። በመድረኩ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንትን ወክለው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ዳዊት ሀዬሶ (ዶ/ር) የአስ/ተማ/አገ/ምክትል ፕሬዝዳንት፤ የሴቶች ትግል ከጥንት ጀምሮ እየተቀጣጠለ እየጨመረ የመጣ ነው ብለዋል።
በጣሊያን ቱሪን ዩኒቨርሲቲ የሚገኙት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከኢትዮጵያ ኤምባሲ ኃላፊዎች ጋር ተወያዩ ዲ.ዩ፦ መጋቢት 06/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ በተማሪዎች የልውውጥ ፕሮግራም በጣሊያን ሀገር ቱሪን ዩኒቨርሲቲ የሚገኙት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች በሀገሪቱ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል። በቱሪን ዩኒቨርሲቲ ለስድስት ወራት ልምድ ለመለዋወጥ ከዲላ ዩኒቨርሲቲ የሄዱት ስድስቱ የሶስተኛ ዲግሪ ተማሪዎች በቱሪን ከተማ በሚገኘው በጣሊያን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ቆንስላ ፅ/ቤት ነው ውይይቱን ያደረጉት። በውይይቱ የኤምባሲው ምክትል ሚሲዮን አቶ አሰፋ አብዩ እና አቶ ደሳለኝ መኮንን የተገኙ ሲሆን ከአምባሳደር ደሚቱ አምቢሳ ለተማሪዎቹ የተላከ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክትን አድርሰዋል።
በአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ሀገር አቀፍ ወስዳችሁ፣ በአቅም ማሻሻያ (remedial) ፕሮግራም ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ወደ ዲላ ዩኒቨርሲቲ የምትገቡበት ቀን ከመጋቢት 14-15/2015 ዓ.ም መሆኑን እንገልፃለን።
ለዲላ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች በሁለንተናዊ ለውጥ አመራር ዙሪያ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ ዲ.ዩ፦ መጋቢት 02/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የሰው ሀብት ልማት ሥራ አመራር ዳይሬክቶሬትና ተቋማዊ ለውጥና መልካም አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በጋራ በመሆን ለበላይ አመራሮች፣ ዳይሬክተሮች፣ ዲኖች እና ቡድን መሪዎች ለተከታታይ ሶስት ቀናት በሁለንተናዊ ለውጥ አመራር (Trasnformational Leadership) ዙሪያ ስልጠና ሰጥተዋል። ዳዊት ሃይሶ (ዶ/ር) የዲላ ዩኒቨርሲቲ የአስ/ተማ/አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት፤ የተቋምን ስኬት በውጤታማነት ከግብ ለማድረስ ከሚሰሩ ስራዎች መካከል አንዱ የአመራርን አቅም መገንባት ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል። ከዚህም አኳያ አመራሮች በትምህርትና በስራ የቀሰሙትን ልምድ ከተቋሙ ነባራዊ ሁኔታ ጋር አጣጥመው ተግባራዊ እንዲያደርጉ ማድረግ እንደሚገባም ገልጸዋል።
ዲላ ዩኒቨርሲቲ በኪነ-ህንፃ ምህንድስና፣ በህክምና እና በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች አስመረቀ ዲ.ዩ፦ መጋቢት 02/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ ዲላ ዩኒቨርሲቲ በቴክኖሎጂና ምህንድስና ኮሌጅ ስር በኪነ-ህንፃ ምህንድስና (አርክቴክቸር) ትምህርት ክፍል፣ በህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በህክምና (ሜዲሲን) ትምህርት ክፍል እንዲሁም በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በዛሬው እለት አስመርቋል። ማቴዎስ ሀብቴ (ዶ/ር) የዲላ ዩኒቨርስቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ተወካይ፤ ለተመራቂ ተማሪዎች፣ ለተመራቂ ወላጆች እንዲሁም ለተማሪዎቹ ለምረቃ መብቃት በተለያየ መልኩ ለተጉ ሁሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በምርምር የበለፀገ የምርጥ ዘር ድንች ለሞዴል አርሶ አደሮች ተሰራጨ ዲ.ዩ፦ መጋቢት 01/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አገልግሎትና አጋርነት ዳይሬክቶሬት በቡሌ ወረዳ ለተመረጡ አርሶ አደሮች በምርምር የበለፀገ የምርጥ ዘር ድንች አሰራጭቷል። ችሮታው አየለ (ዶ/ር) የዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት፤ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የአርሶ አደሩን ህይወት ለመቀየር በማሰብ የተለያዩ ስራዎች ከዞኑ ጋር እየተሰሩ እንደሆነ ገልፀዋል። ዛሬም ለተመረጡ ሞዴል አርሶ አደሮች የምርጥ ዘር ድንች በማሰራጨትና ዘሩን እንዲባዛ በማድረግ ለቀረው አርሶ አደር እንዲዳረስ የማድረግ ስራ ተሰርቷል ብለዋል።
ዓለምአቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) በመላው ዓለም እየተከበረ ነው ዲ.ዩ፦ የካቲት 29/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) የዲላ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች፣ ህፃናት እና ወጣቶች ጉዳይ ዳይሬክቶሬት በዓለምአቀፍ ደረጃ ለ112ኛ ጊዜ እንዲሁም በኢትዮጵያ ደረጃ ደግሞ ለ47ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን ዓለምአቀፍ የሴቶት ቀን አስመልክቶ ተከታዩን መልዕክት ያስተላልፋል።
ለድህረ-ምረቃ አዲስ አመልካች ተማሪዎች የድህረ-ምረቃ ትምህርታችሁን በዲላ ዩኒቨርሲቲ ለመማር ያመለከታችሁ አዲስ አመልካቾች የመግቢያ ፈተና የሚሰጠው ሐሙስ፣ የካቲት 30/2015 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ላይ መሆኑን እየገለፅን አመልካቾች ለፈተና መቀመጥ መቻላችሁን ለመማር ካመለከታችሁበት የትምህርት ክፍል ጋር በመነጋገር በተጠቀሰው ቀንና ሰአት ፈተናውን እንድትፈተኑ እናሳውቃለን። ሬጂስትራር እና አሉምናይ ዳይሬክቶሬት ................... ዲላ ዩኒቨርሲቲ የአረንጓዴው ምድር ዩኒቨርሲቲ
የአንደኛ አመት የጋራ ኮርሳቸውን ላጠናቀቁ ተማሪዎች የትምህርት ክፍል ለመምረጥ የሚረዳ ገለፃ ተሰጠ ዲ.ዩ፦ የካቲት 24/2015 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ) በዲላ ዩኒቨርሲቲ ዋና፣ ሐሴዴላ እና ኦዳያአ ግቢዎች የጋራ ኮርስ (Common Courses) ትምህርታቸውን ተከታትለው ላጠናቀቁ ተማሪዎች የትምህርት ክፍሎችን መርጠው ለመቀላቀል የሚያስችል ገለጻ ተሰጥቷል። በዩኒቨርሲቲው የፍሬሽማን ፕሮግራም ማስተባበሪያ ዲን የሆኑት አስናቀ ይማም (ዶ/ር ) እንደተናገሩት ገለፃው ተማሪዎች የመጀመሪያ አመት ትምህርታቸውን ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ የተዘጋጀ ነው። እንደ ዶ/ር አስናቀ ገለፃ ከሆነ ተማሪዎቹ የጋራ ኮርሶችን ካጠናቀቁ በኋላ ወደ ተለያዩ የትምህርት ክፍሎች ከመግባታቸው በፊት ምርጫቸውን በአግባቡ ለማስተካከል እንዲረዳቸው የወደፊት ሙያቸውን ስለሚወስኑ የትምህርት ክፍሎችና አይነቶች ቅድመ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ገለፃው ይረዳል።