

ዲ.ዩ፦ መስከረም 07/2016 ዓ.ም (ህ.ዓ.ግ)፦ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኮሚኒት ትምህርት ቤት የ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂዷል።
ብቃትና ጥራት ያለው ዜጋ ለማፍራት ትምህርት ለአንድ ሀገር ወሳኝ መሆኑን የገለፁት፤ የኮሚኒቲ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የወላጅና መምህራን ህብረት ሰብሳቢ ዮናታን አየለ(ዶ/ር)፤ ትምህርት ቤቱ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደ ስራ መግባቱን ገልጸው፤ አዲሱን የትምህርት ፖሊሲ ሙሉ በሙሉ ለመተግበር ዝግጅቶች መጠናቀቃቸውን አንስተዋል።
ዶ/ር ዮናታን አክለውም፣ ባለፈው አመት እንደ ሀገር ያለው ውጤት አጥጋቢ ባይሆንም የኛ ትምህርት ቤት አፈፃፀም የተሻለ ነበር ሲሉ አንስተዋል። አሁን ከዞን ባለፈ በክልል ደረጃ ከሌሎች ትምህርት ቤቶች ጋር ለመወዳደር እየሰራን እንገኛለን ሲሉ ዶ/ር ዮናታን ተናግረዋል።
Public and International Relations Directorate
P.O.Box: 419
E-mail: pirdir@du.edu.et
Phone: +251461310001
: +251463312459
The website Developed by DUICT Business App Dev't